Friday, June 13, 2014

የመቐለ ንግደ ቤቶች እና ስያሜዎቻው ‘’ ዲያና ቡና ቤት ‘’ ‘’Diyana coffe house ‘’ ይህን የንግድ ቤት ስም ያየሁት አምና መቐለ እንደመጣን ሃገሩን ለማየት ስዞር ነበር ። ቡና የሀገራችን ባህላዊ መጠጥ ሲሆን ከሌሎች ሀገራት ካለው የሚለየው በአፈላል ስርአቱ ነው ዲያና ቡና ቤትም በባህላችን መሰረት ቡና እይተፈላ የሚሸጥበት ቤት ነገር ግን ስያሜው የእንግሊዟ ልዕልት ነው ። ከታሪክ አንጻር እንኳን ብናይ ልዕልት ዲያና የኢትዮጵያ ቡና የሚተቀዋወቁ እንኳን አይመስለኝም ። ይሄ ትንሽ ምሳሌ ነው ። አብዛኞቹ ንግድ ቤቶች መጠሪያቸወ የምዕራብያውያን ነው ለምን ? ንግድ ቤቶቹን ተወት እናድርግ እና እስቲ እራሳችንን እንመልከት ( የመቐለ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ) ። በወሬያችን መሃል እንግሊዘኛ ጣል ካለደረግን የምንሞት የሚመስለን እንግሊዘኛ አቀላጥፎ የሚናገር ሰውን እንደ ምሁር ስለምናይ የእንግሊዘኛ ትምህርትን ስንማር እንድ ቋንቋች ሳይሆን እንደ ዕውቀት መለኪያ የምናይ ትርጉሙን እንኳን በውሉ የማናውቀውን የእንግሊዘኛ ዘፈን አፍቃሪያን የሆነው ለምንድን ነው ? ምክንያቱም እንግሊዘኛ መናገር ፦ - ኣራዳ - ጎበዝ - ዘመናዊ ሙድ ያለው ( ትክክለኛው የአማርኛ ፍቺው ምንድነው ?) ሙድ ያለን የሆንን ስለሚመስለን ነው ። እንዲሁም አብዛኞቻችን የሃይስኩል ተማሪዎች እያለን እንግሊዘኛ እንማራለን እናጠናለን ነገርግን ኣማርኛ ዞር ብለን አናየውም ( ከተወሰኑ ተማሪዎች በስተቀር ) ። መንግስትም እራሱ በ 12ኛ ብሄራዊ ፈተና ወቅት አማርኛ ሳይኖር እንግሊዘኛ ይፈትናል አማርኛ ያልተፈተነው ስላወቅነው አይደለም እንግሊዘኛ ግን እንደትልቅ ነገር ትምህርት ባለበት ሁሉ ስንማር እንገኛለን ። የኔ ጥያቄ ለምን እንግሊዘኛ ተማርን አይደለም ለምን እንግሊዘኛ ከቋንቋነት በዘለለ መልኩ ትኩረት ተሰጠው ? ነው የኔ ጥያቄ ። በፊት በፊት የቤተሰቦቻችን ስም ስንጠራ ለምሳሌ እናታችንን ፦ እማዬ ፣ እማ ፣ እቴቴ ፣ እታባ ወ.ዘ.ተ አሁን ግን mami , mom , ma ,mother e.t.c እንደዚ እያልን መጥራት ከጀመርን ሰነባብተናል ። ስለዚህ እኛ የዪኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደግሞ የነዚህ የንግድ ቤቶች ቀንደኛ ተጠቃሚ ነን እነዚን ንግድ ቤቶች የሚያስተዳድሩት ሰዎች አብዛኞቹ እንደእኛ ወጣቶች ናቸው ስለዚህ እንሱም እንደእኛ የሰለጠኑ መስሏቸው በእውቀት የመጠቁ ፣ አራዳ ፣ አሪፍ የሆኑ ስለሚመስላቸው ቤቶቹን በባዕድ ሀገር ስም ይሰይሟቸዋል ። በገበያ ደረጃ የሰሩት ስራ በደንብ እደግፋለው ምክንያቱም ስያሜዎቻቸው ከደንበኞቻቸው ፍላጎት የመጡ ናቸው ብዬ አስባለው ። ደንበኛህ የምዕራብያውያን አድናቂ ከሆነ የሱን ፍላጎት ማሟላት ግድ ይላል ። በዚረገድ ንግድ ቤቶች ትክክለኛ የገቢያ( Marketing ) ስራ ሰርተዋል ብዬ አምናለው ። እንደ ሀገር እና እንደ ባህል ትርጉም የሌለው ፣ ባዳነት የሚጎላበት ከ እውቀት የጸዳ ስያሜ ነው ። ‘’ዲያና’’ ስንቶቻችን ነን የምናውቃት ? ለኛስ ምን አድርጋለች ? እነዚህን ጥያቄዎች የሚመልስ የለም ። ሳባ ፣ ጣይቱ ፣ ዘውዲቱ ወ.ዘ.ተ.. እነዚህ ግን ታሪኮቻችን ናቸው ። እነሱን ለንግድ ቤቶች ስያሜ ብናደርጋቸው ስማቸው እንዳይጠፋ ታሪካቸው እንዳይረሳ ይረዳን ነበር ። መጪው ትውልድ ሳባን ታውቃታለህ ሲባል’’ ማነች ? ዘፋኝ ነእ ኦ … አክትረስ ‘’ የሚል አይመስላችሁም ? በመጨረሻም ይህ የባህል ወረራ ከቀጠለ ወደ ማንመለስበት አዘቅጥ ውስጥ ሊያስገባን ይችላል ፤ ለቀጣዩም ትውልድ የምናወርሰው ቋንቋ እንኳን ለማግኘት እንቸገራለን እላለው ። ስለዚህ የሁላችንም ርብ ርብ የሚጠይቅ ስራ በመሰራት የግድ ይለዋል መልዕክቴ ነው ።



                የመቐለ ንግደ ቤቶች እና ስያሜዎቻው  
     ‘’ ዲያና ቡና ቤት ‘’ ‘’Diana coffee house ‘’ ይህን የንግድ ቤት ስም ያየሁት አምና መቐለ እንደመጣን ሃገሩን ለማየት ስዞር ነበር ። ቡና የሀገራችን  ባህላዊ መጠጥ ሲሆን ከሌሎች ሀገራት ካለው የሚለየው በአፈላል ስርአቱ ነው ዲያና ቡና ቤትም በባህላችን መሰረት ቡና እይተፈላ የሚሸጥበት ቤት ነገር ግን ስያሜው የእንግሊዟ ልዕልት ነው ። ከታሪክ አንጻር እንኳን ብናይ ልዕልት ዲያና የኢትዮጵያ ቡና የሚተቀዋወቁ እንኳን አይመስለኝም ። ይሄ ትንሽ ምሳሌ ነው ። አብዛኞቹ ንግድ ቤቶች መጠሪያቸወ የምዕራብያውያን ነው;;
                                    ለምን ?

       ንግድ ቤቶቹን ተወት እናድርግ እና እስቲ እራሳችንን እንመልከት ( የመቐለ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ) ። በወሬያችን መሃል እንግሊዘኛ ጣል ካለደረግን የምንሞት የሚመስለን እንግሊዘኛ አቀላጥፎ የሚናገር ሰውን እንደ ምሁር ስለምናይ የእንግሊዘኛ ትምህርትን ስንማር እንድ ቋንቋች ሳይሆን እንደ ዕውቀት መለኪያ የምናይ ትርጉሙን እንኳን በውሉ የማናውቀውን የእንግሊዘኛ ዘፈን አፍቃሪያን የሆነው ለምንድን ነው ?                                                         
                             ምክንያቱም እንግሊዘኛ መናገር                          
                                                               - ኣራዳ
                                                               - ጎበዝ
                                                               - ዘመናዊ
       ሙድ ያለው ( ትክክለኛው የአማርኛ ፍቺው ምንድነው ?) ሙድ ያለን የሆንን ስለሚመስለን ነው ። እንዲሁም አብዛኞቻችን የሃይስኩል ተማሪዎች እያለን እንግሊዘኛ እንማራለን እናጠናለን ነገርግን ኣማርኛ ዞር ብለን አናየውም  ( ከተወሰኑ ተማሪዎች በስተቀር ) ። መንግስትም እራሱ በ 12ኛ ብሄራዊ ፈተና ወቅት አማርኛ ሳይኖር እንግሊዘኛ ይፈትናል አማርኛ ያልተፈተነው ስላወቅነው አይደለም እንግሊዘኛ ግን እንደትልቅ ነገር ትምህርት ባለበት ሁሉ ስንማር እንገኛለን ። የኔ ጥያቄ ለምን እንግሊዘኛ ተማርን አይደለም ለምን እንግሊዘኛ ከቋንቋነት በዘለለ መልኩ ትኩረት ተሰጠው ? ነው የኔ ጥያቄ ።

በፊት በፊት የቤተሰቦቻችን ስም ስንጠራ ለምሳሌ እናታችንን ፦ እማዬ ፣ እማ ፣ እቴቴ ፣ እታባ  ወ.ዘ.ተ   አሁን ግን  mami , mom , ma ,mother   e.t.c   እንደዚ እያልን መጥራት ከጀመርን ሰነባብተናል ።

      ስለዚህ እኛ የዪኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደግሞ የነዚህ የንግድ ቤቶች ቀንደኛ ተጠቃሚ ነን እነዚን ንግድ ቤቶች የሚያስተዳድሩት ሰዎች አብዛኞቹ እንደእኛ ወጣቶች ናቸው ስለዚህ እንሱም እንደእኛ የሰለጠኑ መስሏቸው በእውቀት የመጠቁ ፣ አራዳ ፣ አሪፍ የሆኑ ስለሚመስላቸው ቤቶቹን በባዕድ ሀገር ስም ይሰይሟቸዋል ።

      በገበያ ደረጃ የሰሩት ስራ በደንብ እደግፋለው ምክንያቱም ስያሜዎቻቸው ከደንበኞቻቸው ፍላጎት የመጡ ናቸው ብዬ አስባለው ።  ደንበኛህ የምዕራብያውያን አድናቂ ከሆነ የሱን ፍላጎት ማሟላት ግድ ይላል ። በዚረገድ ንግድ ቤቶች ትክክለኛ የገቢያ( Marketing ) ስራ ሰርተዋል ብዬ አምናለው ። 

      እንደ ሀገር እና እንደ ባህል ትርጉም የሌለው ፣ ባዳነት የሚጎላበት ከ እውቀት የጸዳ ስያሜ ነው ። ‘’ዲያና’’ ስንቶቻችን ነን የምናውቃት ? ለኛስ ምን አድርጋለች ? እነዚህን ጥያቄዎች የሚመልስ የለም ።

     ሳባ ፣ ጣይቱ ፣ ዘውዲቱ ወ.ዘ.ተ..  እነዚህ ግን ታሪኮቻችን ናቸው ። እነሱን ለንግድ ቤቶች ስያሜ ብናደርጋቸው ስማቸው እንዳይጠፋ ታሪካቸው እንዳይረሳ ይረዳን ነበር ። መጪው ትውልድ ሳባን ታውቃታለህ ሲባል’’ ማነች ? ዘፋኝ ነእ ኦ … አክትረስ ‘’ የሚል አይመስላችሁም ? 

     በመጨረሻም ይህ የባህል ወረራ ከቀጠለ ወደ ማንመለስበት አዘቅጥ ውስጥ ሊያስገባን ይችላል ፤ ለቀጣዩም ትውልድ የምናወርሰው ቋንቋ እንኳን ለማግኘት እንቸገራለን እላለው ። ስለዚህ የሁላችንም ርብ ርብ የሚጠይቅ ስራ በመሰራት የግድ ይለዋል መልዕክቴ ነው ።

’ውዥንብር’’ ምርጥ የማስታወቂያ መንገድ



‘’ውዥንብር’’ ምርጥ የማስታወቂያ መንገድ
      ከሰው ልጅ እጅግ ከሚያስደንቁ ተፈጥሮዎች መካከል ፈጠራ አንደኛው ነው ።  ሰው የሚፈልገውን ነገር ለማግኘት ፣ አላማውን ለማሳካት ፣ ኑሮውን ለማቅለል ብዙ ነገሮችን ይፈጥራል፣እየፈጠረም ነው ወደ ፊትም ይፈጥራል። ውዥንብር አንድ የማስታወቂያ መንገድ አድርጎ ማምጣት እጅግ የተዋጣለት የማስታወቂያ ፈጠራ ነው።

      ልጅ ሆኜ በግቢያችን ውስጥ (አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) ታዋቂ ከሆኑ እንዲሁም ከማይረሱ ልጆች መካከል  ሰርካለም አንዷ ነች ። ሰርካለምን አሁን ድረስ የማስታውሳት ቆንጆ ሆና ፣ ጎነዝ ሆና ወይም የተለየ ነገር ኗሯት አይደለም እሷን ታዋቂ ያደረጋት በአጋጣሚ የተፈጠረ ውዥንብር ነው ፦ ሙሉ ስሟ ሰርካለም ጥላሁን ገሰሰ ነው ። ይህን ልብ ብሎ ያጤነው አንዱ ተማሪ የዘፋኙ ጥላሁን ገሰሰ ልጅ ነች ብሎ አስወራ ከዛን ቀን በኋላ ሁሉም ልጅ ትኩረት የሚሰጣት ልጅ ሆነች ። ጥላሁን ገሰሰን በቲቪ ስናይ የሰርካለም አባት እንል ነበር የሱ ልጅ አለመሆኗን ያወኩት ከረጅም ጊዜ በኋላ አባቷን የማየት እድል ካገኘው ወዲህ ነው እናም ውዥንብር እንደ ማስታወቂያ መጠቀም ለመታወቅ ትልቅ ሚና አለው።

    ድምጻዊ መሃመድ ተሾመ (ድንቢ) ቴዲ አፍሮን እኔ እበልጠዋለው የሚል አስተያየት ሰጠ ተባለ ይህ ከተባለ በኋላእራሱ አስተባበለ ነገር ግን በዚህ ወቅት የ ቴዲ አድናቂዎች ልጁ ላይ ብዙ ስድብ ሲያወርዱበት ቁም ነገሩ ያለው እዚህ ላይ ነው።በመጥፎም ሆነ በጥሩ መሃሙድ በብዙ ሰዎች ዘንድ ሆነ ሰዎችም ቴዲን እንዲህ ያለው እሱ ምን አይነት ዘፋኝ ቢሆን ነው ብለው የሱንም ዘፈኖች ሰሙ በዚህ ሰአት በግርግር መሃሙድ ታዋቂነትን አተረፈ ዘፋኝ መሆኑንም ለብዙዎች አስተዋወቀ።

       ውዥንብር ከማስተዋወቅ( ከማሳወቅ ) አንጻር ትልቅ ጥቅም ቢ ኖረውም ጉዳቱም ያንኑ ያህል ነው። እውቅናን ለማግኘት ተብለው የሚወሩ ወሬዎች ስራቸው ሰፍቶ ወደ አልታሰበ አቅጣጫ ሊያመሩ የሚችሉበትም አጋጣሚ ያንኑ ያህል ነው አንዳንድ ጊዜ አንድን ወሬ ተከትሎ የሚመጣው ነገር ባለጉዳዮቹን ወዳልታሰበ እና ችግር ውስጥ ሲከት ይታያል  

       ውዥንብር እንደማስታወቂያ ይጠቀሙታል ብዬ የማስበው በተለይ አርቲስቶችን ነው ። ዘፋኞች ወይም የፊልም እና የቲያትር ሰሪዎች እንዲታወቁ ከፈለጉ ውዥንብር ዋናው መንገዳቸው ይሆናል ። በ አንድ ወቅት ስሙን በውል የማላስታውሰው አሜሪካዊ ጸሀፊ ሞተ ተብሎ ተወራ ከ ጊዜያት በኋላ ‘’ አልሞትኩም እንዲሁም ለአድናቂዎቼ አዲስ ስራ ይዤ መጥቻለው ‘’ አለ በቃ የሱ መጽሀፍ ለጉድ ተቸበቸበ ። 

    ይህ ውዥንብር አመት ሙሉ ቢያስተዋውቅ ሊገኘው ከሚችለው በላይ በአንድ ወሬ ብዙ ነገርን አገኘ። ከውዥንብር በላይ ባለታሪኩ የሚሰጠው አስተያየት የውዥንብሩ ዋነኛ አካል ነው ። ብዙውን ጊዜ እንደምንታዘበው አንድ ታሪክ ከተፈጠረ በኋላ ባለቤቱ ልክ ነው ወይም አይደለም ብሎ ይናገራል በዚህ ግርግር ትልቅ ማስታወቂያ ይሰራል ።

      የ አለማችን ምርጥ አ እግር ኳስ ተጫዋቾች በእኔ ግምት ውዥንብር በሚገባ ይጠቀማሉ ። ሉበት ክለብ ካልተመቻው በ ወኪላቸው አማካኝነት  ሌላ ክለብ እንደጠየቃቸው ያስወራሉ ይህንን የሚሰሙት ሚድያዎች በ አካል ሲጠይቋቸው አላልኩም ብለው ያስተባብላሉ ። ስለ እነሱ በተደጋጋሚ በተወራ ቁጥር ሌሎች ክለቦች ፍላጎት ያሳድራሉ ጥያቄም ያቀርባሉ።ስለ ተጫዋቹ በተወራ ቁጥር ተፈላጊ ይሆናል።

        ከላይ እንደተገለጸው ውዥንብር ምንም ያህል እውቅናን ማምጣት ቢችልም በ መጥፎ በኩል የተገኘ ስም ግን ይጠቅማል የሚል እምነት የለኝም እንድ ሰው ለመታወቅ ብሎ የጦር መሳሪያ ያዘዋውራል የሚል ውዥንብር በራሱ ላይ ቢፈጥር በሰዎች እና በሚዲያ በደንብ ሊታወቅ ይችላል ቢሆንም ግን ከዛ በኋላ የተረጋጋ እና ሰላማዊ ኑሮ ሊኖር እይችልም ለዚህም ነው ውዥንብር ጥቅም እንዳለው ሁሉ ጉዳቱም ያንኑ ያህል ነው ። ታዲያ በውዥንብር መታወቅ ይሻላል ወይስ በሰራነው ሥራ ልክ ትክክለኛ ማስታወቂያ በመስራት መታወቅ ?  

 

AXE



  AXE
   በአሁኑ ሰአት በአለማችን ቁሳዊነት የሀብት መለኪያ፣የእድገትማሳያ፣ እንዲሁም የስልጣኔ መገለጫ ሆኗል። የአንድን ሰው የኑሮ ደረጃ ለመለካት የሚያሽከረክረውመኪና፣የሚለበሳቸው ልብሶቸ፣የሚኖርበት ቤት፣እንደመስፈርት ይታያሉ። ታዲያ ይህንን መስፈርት ያሟላሰው ሃበታም፣ ተወዳጅ፣ ታዋቂ፣ወዘተ እየተባለ ይጠራል።
     የዕቃዎች ማስታወቂያ በአሁኑ ሰአት ለየት ያለ እና ቁሳዊነት የደላበት ሆኖ እየተሰራ ይገኛል። የአክሰ ዲዮዶራንት ማስታወቂያ ለዚህ አይነት ማስታወቂያ እንደማሳያ ይሆናል። ማስታወቂያው እንደሚያሳየው አንድ ሰው  አክስ ዲዮዶራንትን ሲጠቀም ሴቶች እንደሚቀርቡት ተደርጎ የተሰራ ማስታወቂያ  ነው። ይህ ማስታወቂያ ዘመኑን በትክክል መግለፅ የሚችል ጥሩ ፈጠራ የታየበት ማስታወቂያ ነው።
     ቁሳዊነት በሰፈነበት በአሁኑ ሰአት አንድን ሰወ አክስን ብትጠቀም ሴቶች ይቀርቡሃል ቢባል ግነት አይሆንም። ከላይ ለመጥቀስ እንደሞከርኩት ሰዎች የሚመዘኑት ባላቸው ነገር ስለሆነ ነው።አክስ ደግሞ አራሱን የምርጦች ምርጫ፣ ተወዳጅነትን የሚያስገኝ አድርጎ ከመመልከተ የመነጨ ነው። አክስ ይህንን ማሰታወቂያ መስራቱ በብዙዎች  ዘንድ ሴትን የበታች አድርጎ ከማየት የመነጨ ተደርጎ የታሰባል።
      ሴቶች ብቻ ሳይሆን ወንዶችም ቢሆኑ ጥሩ ልብስ የለበሰች ወይም ሆነ ሎሽን ተቀብታ ሰውነቷ ያማረች ሴትን ሲከተሉ የሚያሳዩ ማስታወቂያዎች ተሰርተዋል። ይህም ማለተ በነሱ አመለካከተ ይህ ማስታወቂያ ወንዶችን ዝቅ አድርጎ ይመለከታለ ማለት ነው።ነገር ግን ማንም ሰው ቢሆን መልካም የሆነ ነገርነ ይወዳል ስለዚህ አክስ የተቀባን ሰው  ሴቶች ቢቀርቡት ምንም ሊገርም የሚችል ነገር አይደለም።
      አክስ የሰራው ማስታወቂያ ከፈጠራ አንፃር ለየት ያለ አየነት ሲሆን ለማስተዋወቅ የተጠቀመበትም መንገድ በጣም ጥሩ የሚባል አይነት ነው። ማስታወቂያ የሚሰራው አስተዋዋቂ ድርጀቱ የኔን ምርት የጠቀማሉ ብሎ ለሚያስባቸው ተመልካቾች ሲሆን የማስታወቂያውም ይዘት የተመልካቹን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ነው። በዚህም በኩል ስናይየአክስ ዲዮራንት ተጠቃሚ ይሆናሉ ተብሎ የሚታሰቡት በሃገራችን አነፃር ወጣቶች በተለይም የከተማ ሰዎች ናቸው። እነዚህም ሊያስደስታቸው እነዲሁም ትኩረት ሰጥተው ሊታተሉት የሚችሉት ማስታወቂያ ልክ እንደ አክሰ አይነት ያልተንዛዛ ትኩረት የሚስብ አይነት ማሰታወቂያ ነው።
      በአሁ ሰአት የሰዎች በአጭር የመግባባት ልምድ እየሰፋ ምጥቷል ( በተለይም በማስታወቂያ)። የአክስ ደንበኞች አክስ የሰራው ማስታወቂያ በአጭሩ ሊረዱት ይችላሉ። በእርሻለሚተዳደር ማህበረሰብ የሚሰራ ማሰታወቂያ ለምሳሌ የማሰዳበሪያ ማስታወቂያ ማብራራት፣ገለፃ ወዘተ ሊያስፈልገው ይችላል ምክንያቱም ይህንንማስታወቂያ የሰራንለት ማህበረሰብ ያለው የመረዳት ወይም የመገንዘብ አቅምን ያማከለ መሆን ስላለበት ነው ነገርግን አክስን ይጠቀማሉ ብለን የምናስባቸው ሰዎች ማብራሪያ ወይም ገለፃ ያለው ማስታወቂያ ብንሰራ ሊሰለቻቸው እንዲሁም ላይመለከቱት ጭምር ይችላሉ ምክንያቱም የምናብራራው ነገር እነሱ ስለሚያውቁት ነው።   
      አበዛኛዎቹ የሃገራችን ማስታወቂያዎች ከአላማ አንፃር ግባቸውን ይበታሉ የሚል ግምት የለኝም። ምክንያቱም ብዙውነ ጊዜ ማስታወቂያዎቹ የሚሰሩት ድራማዊ በሆነ መንገድ ነው ይህ ደግሞ አላማውን ከማሳካት አንፃር አቅሙ አነስተኛ ነው። ምክንያቱም ተመልካቹ ሊመለከት የሚችለው ድራማዊ የሆነውን ነገር ሲሆን መልዕከተን የመስማት አቅሙ ማለትም የዕቃውን አይነት፣አድራሻ ወዘተ ማስታወስ የሚችለው  በጣም አነስተኛ በሆነ መልኩ ብቻ  ነው።
     በአጠቃላይ  አክሰ የሰራው ማስታወቂያ እጅግ ቤጣም ጥሩ እና ለሌሎችም ምሳሌ ሊሆን የሚችል እና ተጠቃሚውንም መሰረት ያደረገ በዘፈቀደ የተሰራ እንዳልሆነ ለማየት አያዳግትም።     
     

ጥሩ እቃ ጥሩ ማስታወቂያ



ጥሩ እቃ ጥሩ ማስታወቂያ
     ሃገራችን በሁሉም ነገር ወደ ሗላ ቀርታለች። በስልጣኔ፣ በእድገት፣በቶክኖሎጂወዘተ ወደ ሗላ ቀርታለች። በማስታወያም ቢሆን ከሌሎች ሃገራት አንጻር በጣም ወደሗላ የቀረች ነች። ለዚህም ምሳሌ ሊሆን የሚችው የሃገራችን ባለሃብቶች እንዱሁም ትልልቅ ድርጅቶች ማስታወቂያ ድርጅታቸውን ለማስተዋወቅ የሚሰራ ሳይሆን እስተዋዋቂውን ለመርዳት ተብሎ የሚሰራ አድርገው ይቆጥሩታል። በነሱ አስተሳሰብ ማስታወቂያ ገንዘብ እንደማባከኛሰ አድርገው ይቆጥሩታል ለአዚህም ምክንያታቸው ጥሩ ምርት ካመረትኩ ምርቴ ጥራት ካለው ማስታወቂያ አያስፈልገኝም ብለው ያምናሉ
 በመጀመሪያ ማስታወቂያ ምንድን ነው ለምንስ ይጠቅማል?
    ማስታወቂያ ማለት የአንድን ድርጅት ምርትይም አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚያስተዋውበት የያሳይበት መንገድ ነው አላማውም፤
       አዲስ ምርት ከሆነ ሰው እንዲያውቀው
       በጥቂቱ የሚታወቅ ከሆነ የንን ለማስፋፋት
        በደንብ የሚታወቅ ከሆነ ባለው ለመቀጠል ደንበኞቹንም የምርቱ ታማኝ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው።
        ምንም ያህል አንድን ምርት በጥራቱ እነደኛ ቢሆንም ነገር ግን ከሱ በጥራት የሚያንሱ ነገር ግን ማስታወቂያ የሚያሰሩ ድርጅቶች በገበያም ሆነ በመታወቅ ይበልጡታል።
        ማስታወቂያ ማለት አንድን ድርጅት ከ ማህበረሰቡ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ማለት ነው። ታዲያ ይህ ድልድይ ከሌለ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ለማሰብ አይከብድም። ስለዚህ ይህ ድልድይ ከሌለ ሰው ወደ ድርጅቱ ለመሄድ ይቸገራል። ኮካኮላ በአለማችን ላይ ካሉ ምርጥ ምርጥ የለስላሳ መጠጦች ውስጥ አንደኛው ነው። ሆኖም ግን ከአመት አመት እነዳስተዋወቀ ነው። ኮካ ኮላ ማስታወቂያ የሚሰራው ጥሩ ምርት ስላልሆነ አይደለም።
         በኢኮኖሚክስ Boom or Peak የሚባል ነገርአለ ይህም ማለት እድገት የመጨረሻው ደረጃ ላይ ሲሆን ማለት ነው። ኮካኮላም በጥራቱም ሆነ በመታወቅ በጣም ትልቅ ደረጃላይ ያለ ድርጅት ነው። ታዲያ ይህንን ያህል ዕውቅና ያለው ለምን ማስታወቂያ ያሰራል ገንዘብስ እያባከነ አይድልም ወይ? የሚሉ ሰዎች አሉ ነገር ግን ማስታወቂያ የሚሰራው ያሉት ደንበኞች ታማኝ ደንበኛ  እንዲሆኑ እና ከዚህ በሗላ የኮካ እጣፈንታ እድገት ሳይሆን ውድቀት ስለሚሆን ባለበት እንዲቀጥል ማስታወያው ስለሚያግዘው ነው።
       አብዛኞቹ በሃገራችን ውስጥ የሚመረቱ ምርቶች በጥራታቸው ከሌሎች ሃገራት ምርቶች ይልቃሉ። ለምሳሌ ጫማ፣ እና የቆዳ ምርቶች አንዳንዶቹ ናቸው። ማህበረሰቡ ግን የሚጠቀመው የሃገሩን ምርት ሳይሆን የቻይና ሴንቴቲክ የሆኑ ውድ ጫማዎችን። በጥራቱ ምርጥ ሆኖ ሳለ ማስታወቂያ ባለመስራቱ እና ባለመታወቁ ገበያ ያጣል እንዲሁም ለኪሳራ ይጋለጣል ምክንያቱም ጥራቱን ጠንካራነቱን ስላልተናገረ።
         ከዚህም በተጨማሪ የግንባታ ባለሙያዎች ለደህንነታቸው ሲሉ በስራ ወቅት የሚጠቀሙት የደህንነት ጫማ አላቸው። ይህ ጫማ የሚሰራው ከ ቆዳ እና ውስጡ ከአደጋ የሚከላከል ብረት አለው። ይህንን ጫማ በሃገራችን ውስጭ በጥራት ይሰራል ነገር ግን ብዙ የግንባታ ባለሙያዎች የሚገዙት የሌሎች ሃገራትን ምርት ነው። ነገር ግን እነሱ የሚጠቀሙት ጫማዎች በሃገራችን ከሚመረቱ ምርቶች
                                             1 በጥራት ያንሳል
                                             2ከንጹህ ቆዳ አይሰራም
                                             3 መጥፎ ጠረን ያመጣል
                                             4 ውስጥ ያለው ብረት እግርን ያሳምማል እና ጠካራ አይደለም  
ሆኖ ም ግን ሰዎች ብዙዉን ጊዜ የሚጠቀሙት ይህንን ከሃገራቸው ምርት በጥራት የሚያንሰውን ምርት ነው። ታዲያ ይህንን የሚያደርጉት ለምን ይበስላችሗል? በጥራቱ የሚበልጠው የሀገራችን ምርት ነው ነገር ግን በተጠቃሚዎች ዘንድ ስለማይታወቅ ሰዎች ይህንን ምርት ሊጠቀሙ አትችሉም። ስለዚህ የሃገራችን ባለሃብቶች ማድረግ ያለባቸው ጥሩ ምርትይ እያመረቱ ጥሩ ማስታወቂያ መስራት ነው። ለጥሩ ምርት የሚያስፈልገው ጥሩ ማስታወቂያ ነውና።   


ጥሩ እቃ ጥሩ ማስታወቂያ
     ሃገራችን በሁሉም ነገር ወደ ሗላ ቀርታለች። በስልጣኔ፣ በእድገት፣በቶክኖሎጂወዘተ ወደ ሗላ ቀርታለች። በማስታወያም ቢሆን ከሌሎች ሃገራት አንጻር በጣም ወደሗላ የቀረች ነች። ለዚህም ምሳሌ ሊሆን የሚችው የሃገራችን ባለሃብቶች እንዱሁም ትልልቅ ድርጅቶች ማስታወቂያ ድርጅታቸውን ለማስተዋወቅ የሚሰራ ሳይሆን እስተዋዋቂውን ለመርዳት ተብሎ የሚሰራ አድርገው ይቆጥሩታል። በነሱ አስተሳሰብ ማስታወቂያ ገንዘብ እንደማባከኛሰ አድርገው ይቆጥሩታል ለአዚህም ምክንያታቸው ጥሩ ምርት ካመረትኩ ምርቴ ጥራት ካለው ማስታወቂያ አያስፈልገኝም ብለው ያምናሉ
 በመጀመሪያ ማስታወቂያ ምንድን ነው ለምንስ ይጠቅማል?
    ማስታወቂያ ማለት የአንድን ድርጅት ምርትይም አገልግሎት ለህብረተሰቡ የሚያስተዋውበት የያሳይበት መንገድ ነው አላማውም፤
       አዲስ ምርት ከሆነ ሰው እንዲያውቀው
       በጥቂቱ የሚታወቅ ከሆነ የንን ለማስፋፋት
        በደንብ የሚታወቅ ከሆነ ባለው ለመቀጠል ደንበኞቹንም የምርቱ ታማኝ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው።
        ምንም ያህል አንድን ምርት በጥራቱ እነደኛ ቢሆንም ነገር ግን ከሱ በጥራት የሚያንሱ ነገር ግን ማስታወቂያ የሚያሰሩ ድርጅቶች በገበያም ሆነ በመታወቅ ይበልጡታል።
        ማስታወቂያ ማለት አንድን ድርጅት ከ ማህበረሰቡ ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ማለት ነው። ታዲያ ይህ ድልድይ ከሌለ ምን ሊፈጠር እንደሚችል ለማሰብ አይከብድም። ስለዚህ ይህ ድልድይ ከሌለ ሰው ወደ ድርጅቱ ለመሄድ ይቸገራል። ኮካኮላ በአለማችን ላይ ካሉ ምርጥ ምርጥ የለስላሳ መጠጦች ውስጥ አንደኛው ነው። ሆኖም ግን ከአመት አመት እነዳስተዋወቀ ነው። ኮካ ኮላ ማስታወቂያ የሚሰራው ጥሩ ምርት ስላልሆነ አይደለም።
         በኢኮኖሚክስ Boom or Peak የሚባል ነገርአለ ይህም ማለት እድገት የመጨረሻው ደረጃ ላይ ሲሆን ማለት ነው። ኮካኮላም በጥራቱም ሆነ በመታወቅ በጣም ትልቅ ደረጃላይ ያለ ድርጅት ነው። ታዲያ ይህንን ያህል ዕውቅና ያለው ለምን ማስታወቂያ ያሰራል ገንዘብስ እያባከነ አይድልም ወይ? የሚሉ ሰዎች አሉ ነገር ግን ማስታወቂያ የሚሰራው ያሉት ደንበኞች ታማኝ ደንበኛ  እንዲሆኑ እና ከዚህ በሗላ የኮካ እጣፈንታ እድገት ሳይሆን ውድቀት ስለሚሆን ባለበት እንዲቀጥል ማስታወያው ስለሚያግዘው ነው።
       አብዛኞቹ በሃገራችን ውስጥ የሚመረቱ ምርቶች በጥራታቸው ከሌሎች ሃገራት ምርቶች ይልቃሉ። ለምሳሌ ጫማ፣ እና የቆዳ ምርቶች አንዳንዶቹ ናቸው። ማህበረሰቡ ግን የሚጠቀመው የሃገሩን ምርት ሳይሆን የቻይና ሴንቴቲክ የሆኑ ውድ ጫማዎችን። በጥራቱ ምርጥ ሆኖ ሳለ ማስታወቂያ ባለመስራቱ እና ባለመታወቁ ገበያ ያጣል እንዲሁም ለኪሳራ ይጋለጣል ምክንያቱም ጥራቱን ጠንካራነቱን ስላልተናገረ።
         ከዚህም በተጨማሪ የግንባታ ባለሙያዎች ለደህንነታቸው ሲሉ በስራ ወቅት የሚጠቀሙት የደህንነት ጫማ አላቸው። ይህ ጫማ የሚሰራው ከ ቆዳ እና ውስጡ ከአደጋ የሚከላከል ብረት አለው። ይህንን ጫማ በሃገራችን ውስጭ በጥራት ይሰራል ነገር ግን ብዙ የግንባታ ባለሙያዎች የሚገዙት የሌሎች ሃገራትን ምርት ነው። ነገር ግን እነሱ የሚጠቀሙት ጫማዎች በሃገራችን ከሚመረቱ ምርቶች
                                             1 በጥራት ያንሳል
                                             2ከንጹህ ቆዳ አይሰራም
                                             3 መጥፎ ጠረን ያመጣል
                                             4 ውስጥ ያለው ብረት እግርን ያሳምማል እና ጠካራ አይደለም  
ሆኖ ም ግን ሰዎች ብዙዉን ጊዜ የሚጠቀሙት ይህንን ከሃገራቸው ምርት በጥራት የሚያንሰውን ምርት ነው። ታዲያ ይህንን የሚያደርጉት ለምን ይበስላችሗል? በጥራቱ የሚበልጠው የሀገራችን ምርት ነው ነገር ግን በተጠቃሚዎች ዘንድ ስለማይታወቅ ሰዎች ይህንን ምርት ሊጠቀሙ አትችሉም። ስለዚህ የሃገራችን ባለሃብቶች ማድረግ ያለባቸው ጥሩ ምርትይ እያመረቱ ጥሩ ማስታወቂያ መስራት ነው። ለጥሩ ምርት የሚያስፈልገው ጥሩ ማስታወቂያ ነውና።